2014 ማርች 17, ሰኞ

ጉዞ ጎንደር (የተማሪነት) አጭር ማስታወሻ (ክፍል አንድ)

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ 60ኛ አመቱን ሊያከብር ነው፡፡ ልዩ ነው አቦ፡፡ እን£ን አደረሰን፡፡ ምናልባት ከቻልኩ እገኛለሁ፡፡ እርግጠኛ ነኝ በርካቶቻችን በዚህ ጊዝ እንደምንገናኝ አስባለሁ፡፡ የቀድሞ ተማሪዎች በዚህ ፕሮግራም ላይ ብትገኙ ደስ ይለኛል፡፡ እኔ በእርግጥም ከልቤ እሞክራለሁ፡፡ ስለሆነም ተውስ አለኝና ለምን ይህችን አልልም ብዬ ተነሳሁ፡፡ ከጉዞዬ ልጀምርና ስለጎንደር ከዚህ ጀምሮ በቻልኩትና ባስታወስኩት ብሎም በማስታወሻዬ ባገኘሁት ልክ እላለሁ፡፡ እነሆ የጎንደር ማስታወሻዬ አንድ ብሎ ቢጀምርስ፡፡

የዛሬ በርካታ ዓመት ወደ|ላ ብዬ የምናገረው ታሪክ ስለኖረኝ ደስ ብሎኛል፡፡ ለመጀመሪያ ግዜ ከተወለድኩባት አዲስ አበባ 734 ኪሎ ሜትር ልንቀሳቀስ ነው፡፡ ጎዞ ጎንደር እነሆ ሊጀመር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የትምህርት ዕድል ነው፡፡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስጄ እድል እጣዬ ከጎንደር አድርሶኛል፡፡ በርካቶች በወቅቱ የት እንደሚደርሰን እንመርጥ በነበረበት በእዛ ሰዓት እኔ በእርግጥም ጎንደር የሚል ነገር አለመምረጤን አስታውሳለሁ፡፡ ከአዲስ አበባ ወጥቼ ስለማላውቅ አዲስ አበባ እንዲደርሰኝ በመመኘት፡፡

ነገር ግን ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆነ፡፡ በወቅቱ ባልሳሳት (በእኛ ግዜ ምደባ በጋዜጣ ይታወቅ ስለበር) ጥቅምት 18 ይመስለኛል ጋዜጣ ላይ ስሜን ያየሁት፡፡ ከዛ በፊት በነበሩት ተከታታ;ይ ሳምንታት በየቀኑ ስሜን ምዕራብ ሆቴል አጠገብ የነበረ ጋዜጣ አዙዋሪ ደንበኛዬ ጋር እየተመላለስኩ የማየው፡፡ ለጋዜጣ ማንበቢያ የምትሆነውን ሳንቲም ደግሞ አባቴ ይሰጠኝ ነበር፡፡ ለነገሩ ጋዜጣ አዙዋሪው፤ ቀደም ሲል አባቴ ይልከኝ ስለነበርና ፖሊስና እርምጃው የሚባለውን ጋዜጣ እየሄድኩ እገዛው ስለነበር አንዳንድ ቀን ሳንቲሙን አይቀበለኝም ነበር፡፡ እኔመ፣ ታዲያ ያቺን ሳንቲም አልተቀበለኝም ብዬ አልመልስም ነበር፡፡ ብቻ ያን ጊዜ፡፡

ከብዙ ጭንቀት ወዲያ ጥምቅምት 18 ቀን ወጣልኝና ስሜን በጋዜጣ አይሁት፡፡ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በሚለው ውስጥ ዝርዝሬ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ብሎ አለሁበት፡፡ ስሜን በምን ፍጥነት እንዳየሁት አላውቅም፡፡ ግን አይሁት፡፡  በጣም ልዩ ስሜት ነበረው፡፡ ወላጅ አባቴን የት እንደደረሰኝ ለመንገር በየቀኑ ፈልጌ ግን ስላልወጣ አልነገረው ስለነበር፡፡ በውስጤ ምደባው አልፎኝ ይሆን እንዴ ብዬ መስጋቴ አልቀረም፡፡ ደርሼ ስመለስ አባቴ ይጠይቀኛል፡፡ አልወጣም የእኔ ብዬ እመልስለታለሁ፡፡ እንድጊህ ነገ ይወጣ ይሆናል ይለኛል፡፡ ይሆናላ እለዋለሁ፡፡ ስሜቴ እንዳይቀየር ያደርግ የነበረው ጥንቃቄ ዛሬም ድረስ ይገርመኛል፡፡ አባቴ በእርግጥም ልዩ ሰው ነበር፡፡ ሀይለኝነቱ ለእኔ ሲሆን አይሰራም ነበር፡፡ ብዙ ስሜቴ እንዲጎዳበት አይፈልግም ነበር፡፡ ስለሆነም ሁሌም ብርታቴ ነበር፡፡ የእናቴን ነገርማ አታንሱት፡፡ ስለእነርሱ ሌላ ጊዜ ብንጨዋወት ይሻላል፡፡

ብቻ እለቱ ደርሶ ስሜም ወጣ፡፡ ህዳር 27 መንቀሳቀሻ ቀን እንደሆነ ይናገራል ጋዜጣው፡፡ አስፈላጊ ያላቸውን ጉዳዮችም ያትታል፡፡ በጣም ምጥን ያለ አሪፍ ማስታወቂያ ነበር፡፡ ብርድልብስ፤ አንሶላ፤ የስፖርት ትጥ፤ ሌሎችም እንዲኖሩ ያዛል፡፡ ትራስ ግን እንዳት;ይዙ፤ ይትራስ ልብስ እንጂ ማለቱን አስታውሳለሁ፡፡ (ለነገሩ ትራስ ይዞ የመጣም ነበር፡፡ የፍሬሽ ነገር)

ቤት ሄድኩ፡፡ እንደወጣ ተናገርኩኝ፡፡ ጎንደር እንደደረሰኝም ተናገርኩ፡፡ ይሄኔ ትንሽም ቢሆን ድንጋጤ በቤቱ ሰፈነ፡፡ ግን ግድ ነው፡፡ የሚ;ያስፈልጉ ነገሮች ተናገርኩ፡፡ በቃ፡፡ የጎንደር ልጅ ልሆን የቀረኝ ወር አካባቢ ነው፡፡ በመሀከሉ ግን ዩኒቨርሲቲው አዲስ ማስታወቂያ አወጣ፡፡ ወደ ታህሳስ 12 ተቀየረ፡፡ በተመሳሳይ ወቅት ኮሜድያን ተስፋዬ ካሣ ያረፈበት ጊዜ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡  አንድ ሴት የኦሮምኛ ሙዚቀኛም ሙት አመት ታስቦ ይውል ነበር፡፡ እኒህ ክስተቶች ትውስ ይሉኛል፡፡
ጉዞ ጎንደር ታህሳስ 10 ቀን ሆነ፡፡ በዚሁ ዕለት ታዲያ መንገደኛ በመሆኔ አውቶብስ ተራ ከለሊቱ 11 ሰዓት ደርሻለሁ፡፡ መድረስ ብቻ አይደለም ነቃ ብያለሁም፡፡ ከት/ቤት ¹ደኞቼ ጋር ነኝ፡፡ እንቅስቃሴ ጀምረናል፡፡ በመንገዱ ሁሉ ልናወራ፡፡ የእናቴንና የአባቴን የመጨረሻ ሽኝት አልረሳውም፡፡ ጉዞ ሆነ፡፡ በርካቶች ከወላጆቻቸው ጋር ሆነው ነበር፡፡ እኔና ¹ደኞቼ ግን ብቻችንን ነበርን፡፡ ስለሆነም ሄድን፡፡

ምሳ በላን፡፡ አሁንም ጉዞ፡፡ በነገራችሁ ላይ አባይ በረሃ ሁለት ሰዓት ወሰደብን፡፡ ተጠምዝዘን እዛው፡፡ ሄደን ሄደን እዛው፡፡ ምንም አይነቃነቅም፡፡ ከባድ ጉዞ፡፡ በእድሜም ልጅነት ስለነበረኝ ነገሮች ሁሉ ይገርሙኝ ነበር፡፡ ግራሞቴ ሳያበቃ ታዲያ ሌላ ግራሞት፡፡  መንገዱ ሰንሰለታማ ነው፡፡ ተራራ እና ገደሉን ማየት ከባድ ነው፡፡ ታንኮች በየቦታው አርጅተው ተጣመው ይታያሉ፡፡ የመኪናችን ረዳቶች (ሁለት ነበሩ) ማብራሪያ እየሰጡን ጉዞ ቀጥለናል፡፡ በውስጤ የቀሩ በርካታ ነገሮች ስላሉ በሌላ ጊዜ እንመለስበት ይሆናል፡፡ ነገር ግን የት ኖራ የሚባል ቦታ ያሉውን ሜዳማ መሬት አይቼ ጠየኩኝ፡፡ ሜካናይዝድ እርሻ እንደነበር ነገሩኝ፡፡ አሁንም ቢሆን ስል አሰብኩ፡፡ አሁን ያለበትን ሁኔታ አላውቅም፡፡ ነገር ግን በቅርቡ ወደ ጅግጅጋ ስሄድ፤ ከጅግጅጋ አልፎ ወደ ሶማሌ ላንድ ባለው መንገድ ላይ አውበሬ ይምትባል ቦታ እስከምደርስ ድረስ ያየሁትን ሜዳ አይቼ፤ ሜካናይዝድ እርሻን ስመኝ፤ የትኖራ ትዝ ብላኝ ነበር፡፡ ግሩም ነበር አቦ፡፡ ጎዞ ጎንደርን ጨርሰን ጎንደር ገብተና፡፡ ታህሳስ 11 ምሽት ላይ ጎንደር ገባን፡፡


በታሪኬ ለመጀመሪያ ጊዜ የሁለት ቀን ጎዞ ተጉዤ ጎንደር ገባሁ፡፡ ምሽት በመሆኑ፤ አብሮኝ የነበረው ወንድወሰን ለታ (ወንዴ) ማደሪያ እስኪፈልግ እቃ እንድጠብቅ ነግሮኝ ግለጋ ሄደ፡፡ ተመልሶ መጣ፡፡ አሁን ዕቃችንን ይዘን ወደ ማደሪያችን ልንሄድ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ መመስገን የሚገባቸው አካላት ነበሩ፡፡ ጉዞዋችን አድካሚ ቢሆንም፤ በወቅቱ የነበሩ ተማሪዎች እኛን ለመርዳት ያሳዩት ቁርጠኝነት ሀያል ነበር፡፡ ምስጋና ብቸራቸው ደስ ይለኛል፡፡ አደረጃጀቱ ምንም ይሁን ምን፤ እርዳታ ያስፈልገን ነበርና ተባብረውናል፡፡ እቃችንን ከማደሪያችን ካኖርን ወዲያ በወቅቱ ሞባይል ስላልነበረኝ በሰላም መድረሳችንን ለቤተሰብ አሳውቀን፡፡ ከዛም ጥቅልል ብለን ገብተን ተኛን፡፡ 

ሲነጋ ከነበረው ደግሞ እንቀጥላለን፡፡ የእዛ ሠው ይበለን፡፡

አብርሃም ተስፋዬ

1 አስተያየት:

  1. I like z way U write! I am proud of U Bro! But Y U made it suspense? I thought U will start immediately from Ur arrival at UoG? :) :) bihonm wedijewalehu ketlbet ! But dnt 4get "የእናቴን ነገርማ አታንሱት" and z poem too!

    ምላሽ ይስጡሰርዝ